አምስቱ አዕማደ ምስጢራት
፩. ምስጢረ ሥላሴ
፪. ምስጢረ ሥጋዌ
፫. ምሥጢረ ጥምቀት
፬. ምስጢረ ቁርባን
፭. ምስጢረ ትንሳኤ ሙታን
፪. ምስጢረ ሥጋዌ
፫. ምሥጢረ ጥምቀት
፬. ምስጢረ ቁርባን
፭. ምስጢረ ትንሳኤ ሙታን
‹‹አምድ›› ማለት ‹‹ምሶሶ›› ማለት ሲሆን ‹‹አዕማድ››ማለት ደግሞ ምሶሶዎች ማለት ነው፡፡
አዕማደ ምስጢር ማለት ደግሞ ‹‹የምስጢር ምሶሶዎች ማለት›› ነው፡፡
እነዚህ ምስጢራት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መሠረታዊ የሆኑ የሃይማኖት አስተምህሮዎች
የሚገለጡባቸው ናቸው፡፡ እነዚህ ምስጢር ለምን ተባሉ ስንል በጣም ረቂቅና የሰው ልጆች ሕሊና መርምሮ ሙሉ ለሙሉ ለመረዳት ከባድ ስለሆኑነው፡፡ እነዚህ ምስጢራት ለክርስቲኖች ብቻ የሚነገሩ በመሆናቸው ነው፡፡
የአዕማደ ምስጢር ምንጭና ስያሜ መሰረቱ ምንድን ነው?
አዕማደ ምስጢራት ይዘት ምንጭ የጌታና የሐዋርያት ትምህርት ነው፡፡
ይሁን እንጅ አነሳሱ በጸሎተ ሃይማኖት ወይም አባቶቻችን ምዕመናንን በትክክለኛው ሃይማኖት ለማጽናትና መናፍቃንን ድል ለመንሳት በተካሄዱ በጉባዔ ኒቂያና ቁስጥንጥንያ ነው፡፡
ከዚህ በኋላ አባቶቻችን ጸሎተ ሃይማኖትን መሰረት በማድረግ ከብሉያት ከሐዲሳትና ከሊቃውንት መጽሃፍት በማውጣጣት አምስቱ አዕማደ ምሥጢራትን አዘጋጅተዋል፡፡
፩. ምስጢረ ሥላሴ
‹‹ሥላሴ››የሚለው ቃል ‹‹ሠለሰ ሦስት አደረገ ››
ካለው የግዕዝ ግዝ የተገኘ ሲሆን ሦስትነት ማለት
ነው፡፡
ይህ ምስጢር የእግዚአብሔርን አንድነት ሦስትነት
የምንማርበት የትምህርት ክፍል ነው፡፡ይህም ልዩ ሦስትነት ይባላል፡፡
ይህም እግዚአብሔር አንድ አምላክ በሦሰት አካል/ኩነታት ወይም ሁኔታዎች/ለአበው፣ ለነቢያት
ለሐዋርያት የተገለጠውን መሰረትበማደረግ ነው፡፡
በአጭር ቃል በባህርይ፣በፈቃድና በስልጣን አንድ
የሆነውን እግዚአብሔር፣የአካል፣የስምና የግብር
ሦስትነት እንዳለው የምናምነው እምነት
ምሥጢር ሥላሴ ይባላል፡፡

