ክፍል ሦስት ‹‹ተዋሥኦተ ቀሲስ አባ ጳውሊ›› (የመጨረሻው ክፍል)



ክፍል ሦስት
‹‹ተዋሥኦተ ቀሲስ አባ ጳውሊ›› (የመጨረሻው ክፍል)
‹‹ዳግመኛም ሕዝቡን፣ ቀሳውስቱን፣ ካህናቱን፣ ሊቃውንቱን እንዲነቅፉ አደርጋለሁ፡፡ ሁላቸውንም ከጽድቅ ሥራ ሰንፈው ለኃጢአት ሥራ እንዲተጉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ንስሓ እንዳይገቡ በውስጣቸው ፍርሃትን፣ ትምክህትን፣ ስንፍናን አሳድርባቸዋለሁ፡፡ በዚህ ምክንያት የወንድሞቻቸውን
ኃጢአት እንጂ የራሳቸውን ኃጢአት አይናዘዙም፡፡ በዚህም ምክንያት ለበደላቸው ሥርየት የላቸውም፡፡ ከኃጢአት እንዳይርቁ በእነርሱ ላይ የማላመጣው ምክንያት የለም፡፡ ምክሬን ከሰሙኝ ፈጽሜ የክርስቶስን ጸጋ አሳጣቸዋለሁ›› አለው፡፡ አባ ጳውሊም ይህን ሰምቶ ፈጽሞ አለቀሰ፡፡ ሰይጣንም አባ ጳውሊ ሲያለቅስ ባየ ጊዜ ደስ አለው፡፡ ይስቅበትም ጀመር፡፡ ‹‹እንደ አንተ ካህናት ናቸውና ስለእነርሱ ታለቅሳለህን?›› አለው፡፡ ‹‹በእውነት ማልቀስ ከወደድክ ስለሊቃውንት፣ ስለደጋግ ነገሥታትና ሥልጣናት፣ ስለመኳንንት፣ ስለገዥዎች መታጣት ፊትህን ጸፍተህ አልቅስ፡፡ ዳግመኛም ስለንጹሐን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ስለኤጲስቆጶሳት፣ ስለቆሞሳትና ስለደጋግ ንጹሐን ካህናት መታጣት አልቅስ፡፡ አብዝተህ ስለቤተ ክርስቲያን በገዳም ስለሚኖሩና ስለገዳማትም አልቅስ፡፡ ይልቁንም ስለወንድሞችህ መነኮሳትን ስለእኅቶችህ መነኮሳይያት ፈጽመህ አልቅስ በኋላ ዘመን ዘመዶቼና ወዳጆቼ አደርጋቸዋለሁና›› አለው፡፡ አባ ጳውሊም ፈጽሞ እያዘነ ‹‹በምን ሥራ እንዲህ ታደርጋቸዋለህ?›› አለው፡፡ ሰይጣንም ‹‹እነርሱ ራሳቸው በፈቃዳቸው ጎዳናዬን ሁሉ ይከተላሉ፣ ፈቃዴንም ይሠራሉ፡፡ የማሳስባቸውንም ይሠራሉ፣ ቃሌንም አይተላለፉም›› አለው፡፡

ኅዳር 21



ኅዳር 21 የሚከበረውን የእመቤታችን በዓል በማድረግ ስለ ታቦተ ጽዮን አሰራርና ምሳሌነት እንዲሁም ስለ ታቦትና ከሀዲዎች ከሁለት መጻህፍት ምንጭ በማድረግ ቃል በቃል የሰፈረ
በዲ/ አውራሪስ በላይ
‟"እኛን ክርስቲያኖች መስለው የገቡ አባታቸው ዲያቢሎስም ካነቀው ስህተት አይርቁም እኛ ግን በእግዚአብሔር ታቦተ ህግ በፅዮን ውስጥ እንስግድ ዘንድ ይገባል፡፡ መጀመሪያዋም እሷ ናት ዛሬም አሁንም እሷ ናት ምሳሌዋም ፍሬዋም የመድሃኒታችን እናት ማርያም ናት፡፡ እንስግድላት ዘንድ የእግዚአብሔር ታቦተ ህግ በእሷ ስም ተባርካለች፡፡" ክብረ ነገሥት
የበዓሉ ምክንያት፡-
ታቦተ ጽዮን በአምስቱ የፍልስጤም ከተሞች ተዓምራቷን ገልጻ 20 ዓመታት በኋላ በድል አድራጊነት ወደ እስራኤል የገባችበት፡፡ 1ኛሳሙ ምዕ5- 6
 ታቦተ ጽዮን የፍልስጤማዊያንን ጣኦት ዳጎንን ያፈራረሰችበት፡፡ 1ኛሳሙ ምዕ5
 ኢትዮጵያዊቷ ንግሥተ አዜብ ሳባ ወደ ፍልስጤም በመሄድ የሰሎምንን ጥበብ ማድነቋና በልጇ በእምነ መለክ (ቀዳማዊ ምኒልክ) አማካኝነት ከሌዋዉያን ካህናት ጋር በመሆን ታቦተ ጽዮን ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገባችበት፤ 1ኛነገ 10 1-13 2ኛዜና መዋዕል 91-12
 ስለ ታቦት ክብር በስፋት የሚገለጥበት
 በሀገራችን በአክሱም የመጀመሪዋ ቤተክርስቲያን አክሱም ጽዮን የታነጸችበት በዓል ነው፡፡
የቃል ኪዳን ታቦት ከመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ነገረ ማርያም በብሉይ ኪዳን ክፍል አንድ
የአምላክ ማደሪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በልዑል እግዚአብሔር ትእዛዝ ጥበብና ማስተዋል በተሰጠው በባስልኤል እጅ በተሰራችው የቃል ኪዳን ታቦት ትምስላለች ይኽቺ
የእግዚአብሔር የጌትነቱ መግለጫ የኾነችው
በፍልስጥኤም ይምለክ የነበረ ጣዖትን ቀጥቅጣ ያጠፋች፤
በድፍረት ሊነካት የሞከረ ኦዛን የቀሰፈች፤
በታላቅ ክብር ወደ ሀገሯ ስትመለስ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በታላቀ መንፈሳዊ ደስታ በፊቷ የዘመረላት
ልጁ ሰሎሞንም ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርቶ በክብር ያኖራት ናት፡፡

ጾመ ነቢያት /ጾመ ድኀነት

“ጾመ ነቢያት /ጾመ ድኀነት” ፡- ከኅዳር 15 እስከ ታኅሣሰ 28 ቀን ያለው ነው፡፡ ጾመ ነቢያት መባሉ ነቢያት ስለጾሙት፤ ጾመ ድኀነት መባሉ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ጠፍቶ ደኀንነት የተገኘበት ስለሆነ ነው። ይህን ጾም የምንጾመው ነቢያት በየዘመናቸው ስለመሲሕ መምጣት በናፍቆት በመጠባበቅ ይጾሙ ይጸልዩ ሰለነበር የእነርሱን አርአያ ተከትለን የክርስቶሰን ልደት ከማክበራችን ቀደም ብለን ይህን ጾም እንድንጾም በሐዋርያት ቤተክርስቲያን ሥርዐት ተሠርቷል፡፡ አጀማመሩ ስንክሳር መንፈቀ ኅዳር ስለሚል ጾሙ ኅዳር 15 ቀን ይጀምራል፡፡ ‘ወጥንተ ዚአሁ መንፈቀ ኅዳር ወፋሲካሁ በዓለ ልደት፡፡‘ መጀመሪያው የኅዳር እኩሌታ ፋሲካው በዓለ ልደት ነው እንዲል፡፡
 “ጾም ቁስለ ነፍስን የምትፈውስ፣ ኃይለ ፍትወትን የምታደክም፣ የበጐ ምግባራት ሁሉ መጀመርያ፣ የጽሙዳን ክብራቸው፣ የድንግልና የንጽሕና ጌጣቸው፣ የንጽሕና መገለጫ፣ የጸሎት ምክንያት እናት፣ የእንባ መገኛ መፍለቂያዋ፣ አርምሞን የምታስተምር፣ ለበጐ ሥራ ሁሉ የምታነቃቃ፣ ሰውነትን በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ትሕትናን ገንዘብ ለማድረግ የምትደረግ መድኃኒተ ነፍስ ናት” ይላታል ሶርያዊው ቅዱስ ይስሐቅ /ማር.ይስሐቅ. አንቀጽ ፬፡ምዕ.፮/፡፡
ጾም ወደ እግዚአብሔር ለተመለሰ ሕዝብ ምልክት ነው፡፡ ‘አሁንስ ይላል እግዚአብሔር በፍጹም ልባችሁ በጾምም በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ፡፡’’ ኢዩ.2፣12፡፡ ‘በጽዮን መለከትን ንፉ ጾምንም ቀድሱ፡፡ጉባኤውንም አውጁ፡፡’’ ኢዩ.2፣15፡፡ አዳም ከማዕረጉ የተዋረደው በመብል ምክንያት ነው፡፡ ዘፍ.3፣1¬-24 ፡፡ ከይሁዳ ወደ ቤተል ተልኮ የነበረው የእግዚአብሔር ሰውም የተቀጣው አትብላ የተባለውን በመብላቱ ነው፡፡ 1ነገ.13፣1¬-34 ፡፡ በአንጻሩም በአስቴር ዘመን አይሁድ ከእልቂት የዳኑት በመጾማቸው ነው፡፡አስ.4፣16¬-17፡፡ ስለዚህ ጸሎት ከጾም ጋር ሲተባበር መልካም ነው ፡፡

ሰይጣን በአባ ጳውሊ ተገዝቶ ሳለ ያወጣው ምሥጢር


 ክፍል ሁለት 

ከዚህም በኋላ አባ ጳውሊ ‹‹ሰዎች ፈጣሪያቸውን እንዲክዱ የምታደርገው በምን መንገድ ነው?›› አለው፡፡ ዲያብሎስም ‹‹ነዚህ ዓለም የማደርገውን ሁሉ ነገርኩህ፤ መጀመሪያ ልጆች የወላጆቻቸውንና የአሳዳጊዎቻቸውን ምክር እንዳይሰሙ ለቃላቸውም እንዳይታዘዙና ‹እናንተ ይልቅ በእውቀት እኛ እንበልጣለን፣ እኛ እናውቃለን› እንዲሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ ዳግመኛም ወላጆቻቸውንና በዕድሜ የሚበልጧቸውን እንዲሳደቡ እናደርጋቸዋለን፡፡ በዚህም ምክንያት የቤተሰብ ፍቅር እናሳጣቸዋለን፡፡ በየሄዱበት ሁሉ እንደተረገሙ ይኖራሉ፡፡ ከዚህም በኋላ በክህደት፣ በዝሙት፣ የምንዝር ጌጥን በመውደድ፣ በስካር፣ በስርቆት፣ ነፍስን በመግደል ፈጽመው እንዲወድቁ እናደርጋቸዋለን፡፡ በመጨረሻም ተስፋ ቆርጠውና አእምሮአቸውን አጥተው ቁጥር የሌለው ኃጢአትን እንዲሠሩ እናደርጋቸዋለን›› አለው፡፡
ዳግመኛም አባ ጳውሊ ‹‹እናንተ አሳቾች እንደሆናችሁ ለሰው በምን ትታወቃላችሁ? መጨረሻችሁስ እንዴት ነው?›› አለው፡፡ ዲያብሎስም ‹‹እንደ አንተ ንጹሕ የሆነ ሁሉ በሥራዬ ያውቀኛል፤ ኃጥአን ግን ሽታዬን ለይተው ሊያውቁኝ አይችሉም፡፡ ለጥቂት ደጋጎች ነው እንጂ ለሁሉ አንታወቅም፣ በመጨረሻ ሥራችን ግን እንተወቃለን›› አለው፡፡
አባ ጳውሊም ‹‹በዕድሜ ያረጀ ዘመኑም የተቃረበና ሥጋውም የደከመን ሽማግሌ በምን ትፈትኑታላችሁ?›› ብሎ ሲይቀው ዲያብሎስም ‹‹እኛ በሽማግሌዎች ብዙ ምክንያት እናገኛለን፡፡ ስንፍና እናመጣባቸዋለን፡፡ ጾም ጸሎትን እንከለክላቸዋለን፡፡ ዘመናቸውን እስኪረግሙና ራሳቸውን እስኪያጠፉ ድረስ የሚያደርስ ጥርጣሬን እናመጣባቸዋለን፡፡ ክፉ ሀሳብና ገንዘብ መውደድን፣ ሰላም ማጣትን፣ ተስፋ መቁረጥን በውስጣቸው እናደርጋለን፡፡ ከልባቸው የሕሊና ጸሎትን ከአንደበታቸው ምስጋናን እናጠፋባቸዋለን›› አለው፡፡

ሰይጣን በአባ ጳውሊ ተገዝቶ ሳለ ያወጣው ምሥጢር

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጻድቁ አባ ጳውሊ ዲያብሎስን ገዝተውት ሳለ ብዙ የሚያስትባቸውን ምሥጢራት በዝርዝር ነግሯቸዋል፡፡ እኔም ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ አንድነት ገዳም ‹‹ተዋሥኦተ ቀሲስ አባ ጳውሊ›› በሚል ርዕስ ያሳተማትን የአባ ጳውሊን ምሥጢር የያዘች እጅግ ድንቅ የሆነች መጽሐፍን ካሁን በፊት በሁለት ክፍል አቅርቤው ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ሦስተኛውንና የመጨረሻውን ክፍል እናያለን፡፡ ነገር ግን በዚህ የጌታችን ታላቅ ጾም ወቅት ጽሑፉ እጅግ ጠቃሚ ከወቅቱም ጋር የሚሄድ ነውና ላላነበቡትም እንዲሆን በማሰብ ከክፍል አንድ ጀምሬ ሦስቱንም ክፍሎች በየተራ እነሆ፡- 
በቅድሚያ ግን ሲነገሩ ብዙ ጊዜ ብንሰማቸውም አባ ጳውሊ ከሚነግሩን ምሥጢራት ጋር የተስማሙ ይሆኑልን ዘንድ እስቲ እነዚህን ቀጥሎ ያሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በደንብ አጢነን እንመልከታቸው፡፡ መልእክታቸውም ምን እንደሆነ በደንብ እንረዳው፡፡ 
‹‹
በመጠን ኑሩ ንቁም፣ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሳ አንበሳ ይዞራልና፡፡ ›› 1 ጴጥ 58፡፡ 
‹‹
እነሆ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፡፡ ›› ሉቃ 2231፡፡ 
‹‹
ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፣ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና፡፡ ›› 1 ዮሐ 38፡፡ 
‹‹
ጻድቅ በጭንቅ የሚድን ከሆነ ዓመፀኛውና ኃጢአተኛው ወዴት ይታይ ዘንድ አለው? ›› 1 ጴጥ 418፡፡
‹‹
በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፣ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ፡፡ ›› ዮሐ 1633፡፡
‹‹
ዓለምንም ሁሉ የሚያስተው ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀድሞው እባብ ተጣለ፣ ለምድርና ለባሕር ወዮቸው፣ ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን እንዳለው ዐውቆ በታላቅ ቁጣ ወደ እናንተ ወርዷልና፡፡›› ራእይ 12፡፡
ሰይጣን በአባ ጳውሊ ተገዝቶ ሳለ ያወጣው ምሥጢር ይህ ነው፡- በመጽሐፉ መግቢያ ላይ የሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ አንድነት ገዳም ያስተላለፈው አጭር መልእክት እንዲህ ይላል፡- ‹‹… ምእመናን የሰይጣንን ክፉ ሥራ ሁሉ ዐውቀውና ተረድተው ከሰይጣን ስሕተት እንዲጠበቁና እንዲማሩበት እንዲሁም ደግሞ ፈተና በሚመጣባቸው ጊዜ ፈተናው የመጣው ከሰይጣን ከሰይጣን መሆኑን ተረድተው ራሳቸውን ለፈተናው እንዲያዘጋጁና በየጊዜውም ራሳቸውን እንዲፈትሹ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግላቸው በማመን ይህን መጽሐፍ በገድሉና በትሩፋቱ ከከፍተኛ የቅድስና ደረጃ ላይ የደረሰውን የቀሲስ አባ ጳውሊን የሰይጣንን ምሥጢር ያጋለጠበትን ድርሳን ከብራናው ገልብጠን ግእዙን ወደ አማርኛ ተርጉመን ምእመናን በቀላሉ እንዲረዱት በሚያስችል ሁኔታ በእግዚአብሔር አጋዥነት አቅርበናል፡፡››

አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ

    የከበረ ገድለኛ አባት የዋልድባው አባ ሳሙኤል የአባቱ ስም እስጢፋኖስ የእናቱ ስም ደግሞ ዓመተ ማርያም ነው። እነርሱም በዘመድ የከበሩ ደጋግ ናቸው፤ እነርሱም በአክሱም ሀገር ሲኖሩ ሁለት ልጆችን ወለዱ። አንደኛው ስሙ...

በብዙ አንባቢያን የተነበቡ